Welcome to
Home ለ2016 የስልጠና ዘመን ለስልጠና የሚሆኑ ግብአቶችን ከማሟላት ጀምሮ በርካታ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች መከናወናቸው ተገለፀ።

ለ2016 የስልጠና ዘመን ለስልጠና የሚሆኑ ግብአቶችን ከማሟላት ጀምሮ በርካታ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች መከናወናቸው ተገለፀ።

06th November, 2023

ጥቅምት 25 ቀን፣ 2016 ዓ.ም
በአዲስ አበባ ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ቢሮ ስር የሚገኙ ኮሌጆች የ2016 በጀት አመት የዝግጅት ምዕራፍ አፈፃፀም ውይይቶች በማካሄድ ላይ ይገኛሉ።
የኮልፌ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ እና የአቃቂ ፖሊ-ቴክኒክ ኮሌጅ የአንደኛ ሩብ አመት የዝግጅት ምእራፍ አፈፃፀማቸውን ለሠራተኛው አቅርበው ሰፊ ውይይት ተካሂዶበታል።
በዝግጅት ምእራፍ ወቅት ለስልጠና ስራው የሚሆኑ ግብአቶችን ከማሟላት ጀምሮ የተለያዩ ማሽነሪዎችን የመጠገን፣ ወርክሾፖችን ለስልጠና የማዘጋጀት፣ ከባለድርሻ አካላት ጋር የስምምነት ሰነድ የመፈራረም እና ሌሎች ወሳኝ ተግባራት መከናወናቸው የተገለፀ ሲሆን በድክመት የታዩ ጉዳዮችም ተነስተው በቀጣይ የተግባር ምእራፍ ወቅት እንዲስተካከሉ አስተያየት ተሰጥቶባቸዋል።
በመድረኮቹ በቀጣዩ የተግባር ምእራፍ ውጤታማ የእቅድ አፈፃፀም ለማስመዝገብ ሠራተኛውና አመራሩ በቅንጅት መስራት እንደሚገባቸው ተመላክቷል።
.

Copyright © All rights reserved.