ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ኃላፊዎች እና ሰራተኞች ገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክን ጎበኙ
ግንቦት 17/2018 ዓ.ም
ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ እና ከ14ቱ ኮሌጅጆች የተውጣጡ ኃላፊዎችና ሠራተኞች በዛሬው እለት ገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክን ጎብኝተዋል።
የጉብኝቱ ዋና ዓላማ በኢንዱስትሪ ፓርኩ ያሉ የሥራ ሂደቶችን፣ የሠራተኛ ክህሎት ፍላጎቶችን እና የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በተግባር መመልከት ነበር። ቡድኑ የፓርኩን የምርት መስመሮች፣ የጥራት ቁጥጥር ሥርዓቶችን እንዲሁም የሠራተኞችን የሥራ ሁኔታ በቅርበት ተመልክተዋል።
.