Welcome to
College 4ኛው ሀገር አቀፍ የክህሎት ውድድር የመክፈቻ ስነ-ስርዓት እየተካሄደ ይገኛል።

4ኛው ሀገር አቀፍ የክህሎት ውድድር የመክፈቻ ስነ-ስርዓት እየተካሄደ ይገኛል።

09th May, 2025

4ኛው ሀገር አቀፍ የክህሎት ውድድር የመክፈቻ ስነ-ስርዓት እየተካሄደ ይገኛል።
በመክፈቻ ስነ-ሥርዓቱ ላይ የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር ተመስገን ጥሩነህን ጨምሮ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባላት ፣ ሚኒስትሮች፣ የተለያዩ የግልና የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ የቴክኖሎጂ እና ፈጠራ ባለሙያዎች እና የውድድሩ ተሳታፊዎች ተገኝተዋል።
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከኢፌዴሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ባዘጋጁት በዚህ ውድድር የክህሎት፣ የቴክኖሎጂ እና የተግባራዊ ጥናትና ምርምር ውድድሮች ይካሄዳሉ።
በተጨማሪም ከውድድሩ ጎን ለጎን በቴክኒክና ሙያ ተቋማት የተመረቱ ቴክኖሎጂዎች ኤግዚቢሽን እና ሞዴል ኢንተርፕራይዞች ምርታቸውን ለገበያ የሚያቀርቡበት ባዛርም ተዘጋጅቷል።

"ብሩህ አዕምሮዎች በክህሎት የበቁ ዜጎች" በሚል መሪ ሃሳብ በኢፌዴሪ የተዘጋጀው ይህ ውድድር ለሚቀጥሉት ስድስት ቀናት ቆይታ ያደርጋል።
.

Copyright © All rights reserved.