Welcome to
College በከተማ አስተዳደሩ የተዋቀረ የሱፐርቪዥን ቡድን የማጠቃለያ ምዕራፍ አፈፃፀም ሱፐርቪዥን ማካሄድ ጀመረ።

በከተማ አስተዳደሩ የተዋቀረ የሱፐርቪዥን ቡድን የማጠቃለያ ምዕራፍ አፈፃፀም ሱፐርቪዥን ማካሄድ ጀመረ።

28th June, 2025

በከተማ አስተዳደሩ የተዋቀረ የሱፐርቪዥን ቡድን የማጠቃለያ ምዕራፍ አፈፃፀም ሱፐርቪዥን ማካሄድ ጀመረ።
ሰኔ 19/ 2017 ዓ.ም
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተዋቀረ የሱፐርቪዥን ቡድን በአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ እና ተጠሪ ተቋማት የ2017 በጀት ዓመት የማጠቃለያ ምዕራፍ የመንግስትና የፓርቲ ስራዎች ዕቅድ አፈፃፀም ሱፐር ቪዥን ማካሄድ ጀምሯል።
የሱፐርቪዥን ቡድኑ በበጀት ዓመቱ በቢሮውና ተጠሪ ተቋማቱ በፓርቲ እና በመንግስት የተከናወኑ ዝርዝር ተግባራት ሪፓርት በማድመጥ ውይይት አካሂዷል።
በበጀት ዓመቱ የተከናወኑ ተግባራት የታለመላቸውን ዓላማ ከማሳካት አንፃር ከቁጥር ባለፈ በህብረተሰቡ ዘንድ ያመጡትን ለውጥ ለማረጋገጥ በጥናት እያስደገፈ ይገኛል ያሉት በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ጥራቱ በየነ ባካሄደው ሪፎርም ተቀራራቢ ግንዘቤ ያለው አመራርና ባለሙያ መፍጠር በመቻሉ የተመዘቡ ለውጦች ማሳያ ናቸው ብለዋል፡፡
የሱፐርቪዥን ቡድኑ በዛሬው ዕለት በቢሮው የተከናወኑ ተግባራት ሪፓርት የያዙ ሰነዶችን በመፈተሽ ላይ ሲሆን በቀጣይ ቀናት በተጠሪ ተቋማትና የተከናወኑ ተግባራት እንደሚፈትሽ ይጠበቃል።
.

Copyright © All rights reserved.